…ከመካከላችሁ ታላቅ መሆን የሚፈልግ ሁሉ አገልጋይ ይሁን፤ ፊተኛ ለመሆን የሚፈልግ ሁሉ፣ የሁሉ ባሪያ ይሁን…ማርቆስ 10:43

1. የዲያቆን ትርጉም

ዲያቆን የሚለው ቃል የመጣው διάκονος (ዲያኮኖስ) ከሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም፦ 

• አገልጋይ፣ አገልጋዮች ወይም ረዳት። 

• እሱ የሚያመለክተው ሌሎችን በታማኝነት የሚያገለግል ሲሆን በተለይም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተግባራዊ እና ደጋፊነት ሚናዎች ውስጥ ነው።

ቁልፍ ቁጥር፡-

‘በአግባቡ ያገለገሉ ለራሳቸው ትልቅ ክብርን፣ በክርስቶስ ኢየሱስም ባላቸው እምነት ብዙ ድፍረትን ያገኛሉ። ‘ 1 ጢሞቴዎስ 3:13

 

 

2. የዲያቆናት ሚና መጽሐፍ ቅዱሳዊ አመጣጥ

የመጀመሪያው የዲያቆናት  አገልግሎት መጀመር  ምሳሌ በሐዋርያት ሥራ 6፡1-7 ይገኛል።

አውድ፡- 

• የቀደመችው ቤተ ክርስቲያን በፍጥነት እያደገች ነበር። 

• አንዳንድ መበለቶች በየዕለቱ በሚደረገው የምግብ አከፋፈል ችላ ይባሉ ነበር። 

• ሐዋርያት በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት ላይ ማተኮር ስለሚያስፈልጋቸው ሰባት ሰዎችን ለማገልገል ሾሙ።

‘ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ መካከል በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ለመሆናቸው የተመሰከረላቸውን ሰባት ሰዎች ምረጡ፤ ይህን ኀላፊነት ለእነርሱ እንሰጣለን፤ እኛ ግን በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንተጋለን።” ‘

ሐዋርያት ሥራ 6:3-4

ቁልፍ ነጥቦች፡- 

መንፈሳዊ መሪዎች በማስተማር እና በጸሎት ላይ እንዲያተኩሩ አገልግሎቱ የተፈጠረው ተግባራዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት ነው። 

• መንፈሳዊ ብስለትን እና ጥበብን ይጠይቃል። 

• የመጀመሪያዎቹ ሰባቱ መካከል እስጢፋኖስና ፊሊጶስ ያካትታሉ፣ በኋላም  ኃያላን አገልጋዮች ሆነዋል።

 

 

3. የዲያቆን መመዘኛዎች

ጳውሎስ በ1ኛ ጢሞቴዎስ 3፡8-13 የተወሰኑ መመዘኛዎችን አቅርቧል።

መስፈርቶች፡ 

1. አክባሪ / የተከበረ – ክብር የሚገባው. 

ዲያቆን ቁምነገር ያለው እና የተከበረ ባህሪ ሊኖረው ይገባል።

በመንፈሳዊ  ምግባራቸው የተነሳ በሌሎች ዘንድ  ክብር ያላቸው ።

2. ባለ ሁለት ምላስ – ሐቀኛ, ሐሜት ወይም አታላይ ያልሆኑ።

3. ሱስ የሌለበት – ራሳቸውን  መግዛት የሚችሉ።

4. ሐቀኟ / ጥቅም ለማግኘት የማይመኝ – በገንዘብ የታመኑ።

5. የእምነትን ምሥጢር በንጹሕ ሕሊና ይዘን – በመንፋሳዊ ትምህርት እና በእምነት ጤናማ የሆኑ። 

6. የተፈተኑ – ከመሾሙ በፊት በባህሪ እና በተለያየ አገልግሎት ተፈትነው የተረጋገጡ። 

7. በቤታቸው  ታማኝ የሆኑ – ቤተሰባቸውን በሚገባ የሚያስተዳድሩ

‘እነርሱም አስቀድመው ይፈተኑ፤ ከዚያም፣ አንዳች ነቀፋ ካልተገኘባቸው በዲቁና ያገልግሉ። ‘ 1 ጢሞቴዎስ 3:10

 

 

4. የዲያቆናት ሃላፊነት

ዲያቆናት በመንፈሳዊ አመራር ላይ እንዲያተኩሩ ፓስተሮች እና ሽማግሌዎች ነፃ የሚያወጡ የቤተ ክርስቲያንን ተግባራዊ ፍላጎቶች ላይ የሚያተኩሩ አገልጋይመሪዎች ናቸው።

ቁልፍ ሚናዎች፡ 

• ችግረኞችን ማገልገል (የሐዋርያት ሥራ 6:1-3) 

• ሀብቶችን ማስተዳደር (የገንዘብ, ቁሳቁስ) 

• የቤተ ክርስቲያን ሥራዎችን መደገፍ 

• አንድነትን ማሳደግ (የሐዋርያት ሥራ 6:5 ሥራቸው ግጭትን እንዴት እንደፈቱ ያሳያል) 

• የቤተ ክርስቲያንን ምእመናን እንክብካቤ እና መርዳት (የታመሙትን መጎብኘት፣ በበጎነትን ስራ ማደራጀት

ዲያቆናት በዋናነት ሰባኪዎች ወይም ውሳኔ ሰጪዎች አይደሉም፣ ይልቁንም ከሽማግሌዎች ጋር አብረው የሚሰሩ አገልጋዮች ናቸው።

 

5. የመጽሐፍ ቅዱስ የዲያቆናት ምሳሌዎች 

• እስጢፋኖስ – በእምነት እና በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ፣ በኋላ በኃይል የሰበከ እና የመጀመሪያው ክርስቲያን ሰማዕት ሆነ (ሐዋ. 6፡8-15፤ ሐዋ. 7)። 

• ፊልጶስ – በዲያቆንነት ያገለገለ እና በኋላም ሰማርያንና ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባን የሰበከ (ሐዋ. 8፡4-40)። 

• ፌበን – በክንክራኦስ ያለች ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ (ዲያቆኖስ) ተብላ ተጠራች (ሮሜ 16፡1)።

 

6. የዲያቆናት አገልግሎት ዓላማ

የዲያቆናት አገልግሎት የሚኖረው፡- 

1. በማስተማር እና በጸሎት ላይ እንዲያተኩሩ ሽማግሌዎችን/ፓስተሮችን የሚያሳርፍ። 

2. ለጉባኤው በተለይም ለአደጋ ተጋላጭ ለሆኑ ( ለሚቸገሩ) ሰዎች እንክብካቤን መደረጉን የሚያረጋግጡ። 

3. ግጭቶችንና ፍላጎቶችን በፍትሃዊነት በማሟላት የቤተ ክርስቲያንን አንድነት የሚያጎለብቱ። 

4. “ለመገልገል ሳይሆን ለማገልገል” የመጣውን የክርስቶስን  ኢየሱስን  በሚያንፀባረቅ  አገልግሎት ሞዴል የሚሆኑ (ማርቆስ 10፡45)።

የመጨረሻ መልእክት፡-

* ዲያቆን ከሆንን – በትህትና እና በደስታ በታማኝነት እናገልግል። 

* የጉባኤው አካል የሆናችሁ – ዲያቆናቶቻችሁን ደግፉ እና ስራቸውን አክብሩ። 

* ይህንን ጥሪ እያሰባችሁ ከሆነ – ባህሪዎቻችሁን መርምሩ እና የእግዚአብሔርን ምሪት ፈልግ።

 

Scroll to Top